የዛሬውን የአፍሪካን ቀን ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባን ኪ ሙን ዛሬ ባወጡት መግለጫ፤ ሰብአዊ መብትን ሙሉ በሙሉ ማስከበር የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ ነው ብለዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ዕለቱ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1963ዓ.ም በዚህ እለት ከቅኝ ግዛቶት ነፃ የወጡ 32 የአፍሪካ አገሮች መሪዎች የአፍሪካን ህብረት ቻርተር የፈረሙበትም ነው።
የዛሬውን የአፍሪካን ቀን ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባን ኪ ሙን ዛሬ ባወጡት መግለጫ፤ ሰብአዊ መብትን ሙሉ በሙሉ ማስከበር የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ ነው ብለዋል።
On #AfricaDay2016, #UNSG Ban urges leveraging gains to ensure ‘no African is left behind’ https://t.co/g64ORN4Fxm pic.twitter.com/vlzDIFLKd6
— UN News Centre (@UN_News_Centre) May 25, 2016
የዘንድሮው የአፍሪቃ ቀን ክብረ በዓል፤ በአጠቃላይ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ፤ በተለይም የሴቶች መብት ከበሬታ እንዲረጋገጥ ትኩረት ይጠይቃል።
በሴኔጋል በሚገኘው የተ.መ.ድ. የሴቶች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የምእራብ እና መካከለኛ አፍሪካ ክፍሎች የሴቶችን አቅም ለማጎልበት በተነጣጠሩ ፕሮግራሞች ላይ የሚሰሩትን የቤ ዲያሎን (Yébé Diallo) ሳሌም ሰለሞን ማምሻውን በስልክ አነጋግራለች። ዝርዝሩን ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5