ዛሬ እለቱ የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተበት 53ተኛ ዓመት የሚከበርበት ነው

የአፍሪካን ህብረት /ፋይል ፎቶ/

የዛሬውን የአፍሪካን ቀን ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባን ኪ ሙን ዛሬ ባወጡት መግለጫ፤ ሰብአዊ መብትን ሙሉ በሙሉ ማስከበር የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ ነው ብለዋል።

ዕለቱ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1963ዓ.ም በዚህ እለት ከቅኝ ግዛቶት ነፃ የወጡ 32 የአፍሪካ አገሮች መሪዎች የአፍሪካን ህብረት ቻርተር የፈረሙበትም ነው።

የአፍሪካ አገሮች መሪዎች በአፍሪካ ህብረት ዋና ጽ/ቤት /ፋይል ፎቶ/

የዛሬውን የአፍሪካን ቀን ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባን ኪ ሙን ዛሬ ባወጡት መግለጫ፤ ሰብአዊ መብትን ሙሉ በሙሉ ማስከበር የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ ነው ብለዋል።

የዘንድሮው የአፍሪቃ ቀን ክብረ በዓል፤ በአጠቃላይ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ፤ በተለይም የሴቶች መብት ከበሬታ እንዲረጋገጥ ትኩረት ይጠይቃል።

በሴኔጋል በሚገኘው የተ.መ.ድ. የሴቶች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የምእራብ እና መካከለኛ አፍሪካ ክፍሎች የሴቶችን አቅም ለማጎልበት በተነጣጠሩ ፕሮግራሞች ላይ የሚሰሩትን የቤ ዲያሎን (Yébé Diallo) ሳሌም ሰለሞን ማምሻውን በስልክ አነጋግራለች። ዝርዝሩን ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ዛሬ እለቱ የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተበት 53ተኛ ዓመት የሚከበርበት ነው