አዲስ አበባ —
በሕገወጥ ሰዎች ዝውውር ምክንያት ዛምቢያ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙት ዜጎቹ 1መቶ አሥራ ሥምንት መሆናቸውን የጠቆመው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲፈቱና ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ከአሥራ ሁለት ቀናት በፊት ነው 70 ኢትዮጵያውያን በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ምክንያት ዛምቢያ ውስጥ መታሰራቸው የተገለፀው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው ደግሞ፣ ከእነሱ ቀደም ሲል የተያዙትን ጨምሮ ቁጥራቸው 1መቶ አሥራ ሥምንት ደርሷል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ