የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፌዴራል ምርመራ ቢሮ /ኤፍቢአይ/ ዳይሬክተሩን ጄምስ ኮሜይን ለማባረር የወሰኑት በራሣቸው ቃላት “መሥራቤቱን በተሳካ ሁኔታ ለመምራት ባለመቻላቸው” እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ይሔንን የዋሺንግተንን የፖለቲካ መንደር ሁሉ ያስደነገጠ የትናንት ምሽት ድንገተኛ እርምጃቸውን ለኮሜ በድብዳቤ ያሳወቋቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለውሣኔያቸውም መሠረት የሆኗቸው ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ጄፍ ሴሼንስ እና ምክትላቸው ሮድ ራዥንስቲን በቀድሞዋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄላሪ ክሊንተን የኢሜል አጠቃቀም የተያዘውን ምርመራ በሚገባ መምራት ባለመቻላቸው ከሥልጣናቸው እንዲባረሩ በተናጠል ያቀረቡላቸው ደብዳቤዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ