በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኒውዮርክ የፀጥታና የደህንነት ሁኔታ ጥብቅ ሆኗል


ዶናልድ ትራምፕና ሂላሪ ክሊንተን
ዶናልድ ትራምፕና ሂላሪ ክሊንተን

ኒውዮርክ ከተማ ነገ ማክሰኞ ከሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዋዜማ የሁለቱን የዋና ዋና ፓርቲ ዕጩዎች ለማስተናገድ እየተሰናዳች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የከተማይቱና የፖሊስ ባለስልጣናት የዕጩዎቹን ደህንነት ለማረጋገጥ በትጋት በመሥራት ላይ ናቸው፡፡

የማራቶን ሯጮችና አድናቂዎቻቸውን፤ እንዲሁም ለምርጫ ዘመቻ የተሰማሩትን የሁለቱን ዕጩዎች ደጋፊዎች ጨምሮ ሁሌም እንግዳ የማታጣና ድምቀት የማይለያት ከተማ ከመቼውም በላይ በሠው ጎርፍ ተጥለቅልቃለች።

ይህ ሁሉ ዓለምአቀፉ አሸባሪ ቡድን አልቃይዳ ጥቃት ሊሰነዝር ሊያቅድ ይችል ይሆናል የሚል የፀጥታ ጥንቃቄ አስፈላጊነት ወሬ እየተሰማ ባለበት ነው።

“ቢግ አፕል” በሚለው ዘመን የጠገበ የቁልምጫ ሥሟ የምትታወቀውን ከተማ ደማቅ ገጽታና ባለ ቀለም ድምፆች በተመለከተ የአሜሪካ ድምጿ ካሮሊን ፐርሱዩት ዘገባ አድርሳናለች።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በኒውዮርክ የፀጥታና የደህንነት ሁኔታ ጥብቅ ሆኗል
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:26 0:00

XS
SM
MD
LG