በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

74 የምክር ቤት አባላትና 47 ሴናተሮች ለጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ደብዳቤ ጻፉ


የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላትና ሴናተሮች የኢትዮጵያ መንግሥት ዓለም አቀፍ የሕጻናትን ጉዲፈቻ እንዲቆም የሚያስገድደውን ውሳኔ በድጋሚ እንዲያጤነውና በሕጋዊ መንገድ የጉዲፈቻ አሠራር ጀምረው በሂደት ላይ ያሉ ቤተሰቦች ጉዳያቸውን እንዲጨርሱ እንዲደረግ ለኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ጻፉ።

የምክር ቤቱ አባላትና ሴናተሮቹ በጻፉት ደብዳቤ፤ «ኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ጉዳይ ላይ ወደፊት የምትከተለውን ፖሊሲ አስመልክቶ መንግሥትዎ የወሰደውን ውሣኔ እያከበርን ቀደም ሲል ተጀምረው እስከ ሚያዝያ 13/2009 ዓ.ም እንቅስቃሴ ላይ ለነበሩ ጉዳዮች የሚሰጠው መፍትኄ እንዲፋጠን ለማድረግ እገዛዎን እንዲያደርጉልን እንጠይቃለን፡፡ እነዚህ ሕፃናት ከአሳዳጊ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ በመርዳት በኩል ከእኛ ጋር ያለመተባበር በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ግንኙነት እንዳይጎዳው እንሠጋለን፡፡» ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በጉዳዩ ላይ የሚሰጠውን ምላሽ ይዘን እንመለሳለን።

74 የምክር ቤት አባላትና 47 ሴናተሮች ለጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ደብዳቤ ፃፉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:39 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG