አዲስ አበባ —
UNOCHA Logo
ምሥራቅ አፍሪካ ላይ በደረሰው ድርቅ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ኢትዮጵያዊያን ትክክለኛ ቁጥር የሚታወቀው ሰሞኑን ከሚጀመረው ግምገማ በኋላ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ አስታወቀ፡፡
በያዝነው የአውሮፓ 2017 ዓመት መጀመሪያ ላይ የወጣው የሰብዓዊ ድጋፍ መጠየቂያ ሰነድ በዚህ ግምገማ መሠረት እንደሚከለስ የቢሮው ቃል አቀባይ ቾይዝ ኦኮሮ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር 2.2 ሚሊዮን መጨመሩ ይፋ የተደረገው ሰሞኑን ነው፡፡ በዚህም መሠረት 5.6 ሚሊዮን የነበረው ቁጥር 7.8 ሚሊዮን ደርሷል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
-
እስክንድር ፍሬው