ዋሺንግተን ዲሲ —
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት በዋርሶው ፖላንድ ባደረጉት ንግግር የምዕራባውያን እሴት ለጥቃት ዒላማ ሆኗል፣ ምዕራባዊያን ግን ለመከላከል ዝግጁ መሆናቸው አጠያያቂ ነው ብለዋል፡፡
በዚህ በሁለተኛው የአውሮፓ ጉዟቸው በተለይ ሩሲያ ላይ የተቃጣ በዩክሬን እና በሶሪያ የማናጋት እርምጃ ያሉትን ጭምሮ ጠንካር ያለ ንግግር አስምተዋል፡፡
ፖላንድ ቃል እንደገባችው ህዝቧ ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሞቅ ያለ አቀባበል አድርጓል፡፡
በዋርሶ አመፅ ጊዜ ናዚን ሲዋጉ ለተሰዉት ዜጎች ከቆመው ሃውልት ፊት ለፊት ባደረጉት ንግግር ፕሬዚዳንቱ አስተናጋጇን አገር አወድሰዋል፡፡
ከዋርሳው ሄነሪ ሪጂዌል ያላከው ዘገባ ነው፡፡
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ