መቀሌ —
በትግራይ ክልል የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ተብሎ በወጣው ዐዋጅ እንዲዘጉ ተወስኖ የነበሩ አንድ አንድ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዳግም እንዲከፈቱ የክልሉ የወረርሽኙ መከላከል ኮማንድ ፖስት ወስኗል።
በአንድ ወረዳ ውስጥም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ የተፈቀደ ሲሆን የሚበዙ የመንግሥት ሰራተኞችም ወደ ሥራ እንዲመለሱ ተወስኗል።
ውሳኔው ከነገ ቅዳሜ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ምክትል ረዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።