አዲስ አበባ —
የሁለገቡ እና የአንጋፋው ባለ ተሰጠዖው የኪነጥበበ ሰው የአቶ ተስፋዬ ሣህሉ (የአባባ ተስፋዬ) አስከሬን ሽኝት ትናንት በመንበረ ፀባዖዎት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መካነ መቃብር ተፈፅሟል፡፡
አርባ ሁለት ዓመታት በቴሌቪዥን መስኮት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ልጆች ወላጆች ፊት፣ እርሳቸው በእነዚህ ዓመታት በርካቶች ዘንድ ደርሰዋል፣ ከቤታቸው ቤተኛ ሆነዋል፡፡
ሩቅ ሆነው እንደ ቅርብ፣ ባዕድ ሆነው እንደ ዘመድ፣ የቅርብ ረዳት፣ የልጆች የግብረ ገብ መምህር ሆነው አበባ የነበሩት ልጆች ፍሬ ሲሆኑ ተመልክተዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ