በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሶማሊያው ፕሬዝደንት በኤርትራ የነበራቸውን ጉብኝት አጠናቀቁ


የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኤርትራ የነበራቸውን የሁለት ቀናት ጉብኝታቸውን በማጠናቀቅ ዛሬ ረፋድ ላይ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ አሸኛኘት ሲያደርጉላቸው፤ አስመራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፤ ኤርትራ፤ እአአ 26/2024
የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኤርትራ የነበራቸውን የሁለት ቀናት ጉብኝታቸውን በማጠናቀቅ ዛሬ ረፋድ ላይ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ አሸኛኘት ሲያደርጉላቸው፤ አስመራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፤ ኤርትራ፤ እአአ 26/2024

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ በኤርትራ የነበራቸውን የሁለት ቀናት ጉብኝት አጠናቀዋል።

ሶማሊያ የተረጋጋች መሆኗን ማረጋገጥ የቀጠናውን ሠላምና መረጋጋት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን የሁለቱ ሃገራት ፕሬዝደንቶች በውይይታቸው ማጠቃለያ ላይ መግለጻቸው ታውቋል።

በቀናው ግጭትና ሁከት ከሚፍጥሩ የውጪ ጣልቃ ገብነቶች ራሱን ማላቀቅ እንዳለበት የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ማሳሰባቸውን የሃገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር መግለጫ አመልክቷል።

የሶማሊያው ፕሬዝደንት በበኩላቸው ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ በበኩላቸው ኤርትራ የሃገራቸውን ብሔራው ሠራዊት ለማተናከር ለምታደርገውን አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

የፕሬዝደንት ሃሳን ጉብኝት የመጣው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ በመካከላቸው ያለውን ውጥረት ለማርገብ ከሁለት ሳምንታት በፊት አንካራ ላይ ሥምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ ነው።

ሁለቱ ሀገራት አንዱ የሌላውን ሉአላዊነት፣ እንዲሁም የግዛት አንድነት እንደሚያከብር በፈጸሙት ሥምምነት አስታውቀዋል። ሁለቱ ወገኖች በተጨማሪም ኢትዮጵያ ለንግድ ጠቀሜታ የባሕር አቅርቦት እንዲኖራት ውይይት እንደሚያደርጉ ተስማምተዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ከሁለት ዓመታት በፊት ከተመረጡ ወዲህ አሥመራን ሲጎበኙ ለስምንተኛ ጊዜ ነው።

ኤርትራ በርካታ የሶማሊያ ጦር ዓባላትን በማሠልጠን ላይ ስትሆን፣ የተወሰኑት ሥልጠናቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው በመመለስ በአል ሻባብ ላይ በሚወሰደው እርምጃ በመሳተፍ ላይ ናቸው።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG