አዲስ አበባ —
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ወሳኝ የሆነ የለውጥ ሂደት መጀመሯን በርካታ የበጎ ፈቃድ ሰዎችን እንደምትፈልግ ታዋቂ ምሁራንና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ፓ/ር መስፍን ወ/ማርያም አሳስበዋል፡፡
እያንዳንዱ ሀገር ወዳድ ዜጋም ለተጀመረው ለውጥ ድጋግ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ ይህን መልዕክት ያስተላለፉት ለመብቶች ተሟጋቹና በግብረ ሰናይ ለሚታወቀው ለአቶ ኦባንግ ሜቶ አቀባበል በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ላይ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ተያይዘው ወደ ገደል ከመውደቅና ወደ ተራራ ከመውጣት መምረጥ ያለባቸው ጊዜ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን እንደ አቶ ለማ መገርሣና ዶ/ር አብይ አሕመድ ያሉ መሪዎችንም እንዲደግፉ መክረዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ