WASHINGTON DC —
የዩናይትድ ስቴይትስ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ በአፍሪካ፤ በኢትዮጵያና ኬንያ የሚያደርጉት ጉብኝት አንዱ አካልየሆነው የንግድና መዋእለንዋይ ግንኙነት ነው።
ዩናይትድ ስቴይስትስ ከኢትዮጵያ ጋር በሀይል ልማት፣ ግብርና፣ ንግድ፣ ጤናና ሌሎች ዘርፎችም ለመተባበር የሚያስችሏት ፖሊሲዎችን ቀይሳ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረች ቆይታለች። ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጸጥታና ደህንነት እንዲሁም ከዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ባሻገር የምጣኔ ሀብት ግንኙነት ላይ ያተኩራሉ።
የንግድና ምጣኔ ሀብት አዘጋጅ ሔኖክ ሰማእግዜር ከ30 ዓመታት በላይ በዓለም ባንክና ሌሎች የዓለም አቀፍ ልማት ድርጅቶች የሰሩ ባለሙያ በእንግድነት ይዟል።
ዶር አክሎግ ቢራራ በቅድሚያ የፕሬዚደንት ኦባማን የኢትዮጵያ ጉዞ ወሳኝ አምዶች በማብራራት ይጀምራሉ።