አዲስ አበባ —
በኦሮሚያ ክልል አያሌ ከተሞች የንግድ ሱቆች ተዘግተው መዋላቸው ታወቀ፡፡ በአንዳንድ ከተሞች የሱቅ ባለቤቶች በግድ እንዲከፍቱ ተደርገዋል ተባለ፡፡
ለዚህ የሥራ ማቆም አድማ መንስዔዎቹ ከአቅም በላይ ተጥሏል የተባለውን ግብርን ጨምሮ የተለያዩ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ የሕዝብ ጥያቄዎች እንደሆኑም ቪኦኤ ያነጋገራቸው ሰዎች ገልፀዋል፡፡
ቪኦኤ ከተለያዩ ምንጮች መረዳት እንደቻለው በአዲስ አበባ አቅራቢያ ከሚገኙ የኦሮሚያ ከተሞች አንስቶ በደቡብ፣ በሰሜንና በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ከተሞች የንግድ ሱቆች ዛሬ ተዘግተው ውለዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ