ዋሽንግተን ዲሲ —
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማና የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ትላንት የዓለሙን መድረክ ለረዥም ጊዜ ሲያነታርካቸው በቆዩ የሦሪያና የዩክሬን ግጭቶች ላይ ያሏቸውን ልዩነቶች ለማስረዳት ተጠቅመውበታል።
መሪዎቹ በጠቅላላው ጉባዔ ወቅት በጎን ተገናኝተው ሲነጋገሩ አብዛኛውን ጊዜ የወሰዱት በሁለቱ ጉዳዮች ላይ መሆኑ ተዘግቧል።
ሚስተር ኦባማና ሚስተር ፑቲን በይፋ ተገናኝተው ሲነጋገሩ ከሁለት ዓመታት በሁዋላ ትላንት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
የአሜሪካ ድምፅ የዋይት ሃውስ ቤተ መንግሥት ዘጋቢ አሩ ፓንደ (Aru Pand) ያጠናቀበረችው ሪፖርት አለ።
ሰሎሞን ክፍሌ ያቀረበው ዘገባን የተያያዘውን ፋይል በመጫን ያዳምጡ።