በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ተመስገን ሕመሙ ፀንቶበታል” የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

በዝዋይ ማረሚያ ቤት የሦስት ዓመት እስራት ተፈርዶበት የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሕመሙ ፀንቶበት ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እንደነበር የገለፁት ቤተሰቦቹ፤ የማረሚያ ቤት ባለሥልጣናት የጤንነት ሁኔታውን አስመልክቶ መረጃ እንደከለከሏቸው ቤተሰቦቹ አስታወቁ።

በስም ማጥፋት፣ ሕዝብን በማነሳሳትና ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ክስ የሦስት ዓመት እስራት የተፈረደበትን ጋዜጠኛ እስራት የመብት ድርጅቶች ሲያወግዙና ጋዜጠኛው እንዲፈታ ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።

ተመስገን ከዚህ ቀደም በእስር ላይ የሕክምና አገልግሎት ተከልክሎ እንደነበር የጋዜጠኛ ተሟጋች ቡድኑ/CPJ/ በተደጋጋሚ መዝግቧል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

“ተመስገን ሕመሙ ፀንቶበታል” የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:52 0:00

XS
SM
MD
LG