በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጋዛ ድንበር ግጭት ዛሬም ቀጥሏል


በእሥራኤል የጋዛ ሠርጥ ወሰን ላይ ዛሬ በተነሣ ግጭት ቢያንስ አንድ ፍልስጥዔማዊ ተገድሎ ሌሎች ቁጥራቸው አርባ የሆነ ሰዎች ቆስለዋል። ግጭቱ የተፈጠረው ከአንድ ሣምንት በፊት በዚያው አካባቢ ተካሂዶ በነበረ ሁከት የበረታበት የተቃውሞ እንቅስቃሴ 19 ፍልስጥዔማዊያን በእሥራኤል ወታደሮች መገደላቸውን ተከትሎ ነው።

በሺሆች የሚቆጠሩ ፍልስጥዔማዊያን ወደ ጋዛ ወሰን አካባቢ መጉረፋቸውና እዚያ ሲደርሱም የእሥራኤል ወታደሮች ከኃይል ጋር እንደተቀበሏቸው ተዘግቧል።

ሰልፈኞቹ የድንበሩን አጥር እንዳይጥሱ ለማቆም በሚል ወታደሮቹ አስለቃሽ ጋዝ፣ የጎማ ጥይቶችና በእውን የእርሣስ ጥይቶች ተኩስ ከፍተውባቸዋል።

የዛሬውንና መሰል ጥቃቶችን ‘ከመጠን ያለፈ ኃይል ነው’ ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች አውግዘውታል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የጋዛ ድንበር ግጭት ዛሬም ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:22 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG