በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"መከላከያው የኔ አይደለም የሚለው ሕዝብ የለውም" - ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ


ጦር ኃይሎች ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ
ጦር ኃይሎች ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ

የሃገሪቱ ጦር ኃይሎች ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ ስለ ሕገ ወጥ የመሳሪያ ዝውውርና ስለ መከላከያ ዩኒፎርም ተጠይቀዋል። ምዕራብ ኦሮሚያ፣ ምዕራብ ጎንደርና ትግራይ መከላከያው የወሰደው እርምጃና ያሳየው ትዕግስት አድሎአዊ ነው ስለመባሉም ተጠይቀዋል።

“ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ያለመረጋጋት አጋጣሚ በመጠቀም ራሳቸውን በገንዘብ ማበልፀግ የሚፈልጉ ሰዎች በጦር መሣሪያ ንግድ ላይ ተሠማርተው ተገኝተዋል” ሲሉ የሃገሪቱ ጦር ኃይሎች ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ ለቪኦኤ ገልፀዋል። ይህ ሁኔታም በተለያየ ቦታ “ሕገወጥ የመሣሪያ ዝውውር እንዲኖር መንገድ ከፍቷል” ብለዋል።

ለሁለቱም ችግሮች መፍትኄ ለማግኘት መንግሥታቸው እየሠራ መሆኑን የጦር አዛዡ ተናግረዋል። ጄኔራል ብርሃኑ በሃገሪቱ የፀጥታ ሁኔታ ላይ በዚህ ሣምንት ፓርላማው ፊት ቀርበው የሰጡትን ማብራሪያ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በምዕራብ ኦሮምያ፣ በትግራይና በአማራ ክልሎች ውስጥና በመካከላቸውም ያለውን የፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ መሥሪያ ቤታቸው ሰሞኑን ስለሚሠነዘሩበት ወቀሳዎች፤ እንዲሁም ካለመረጋጋቱ ጋር ተያይዞ ‘የአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አስተዳደር አገሪቱን መምራት አቅቶታል’ እየተባለ ስለሚወራው ጉዳይ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

"መከላከያው የኔ አይደለም የሚለው ሕዝብ የለውም" - ምክትል ኤታ ማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ
please wait

No media source currently available

0:00 0:17:06 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG