በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኮቪድ ስጋት ክሊኒኮችን የሸሹ የሶማሊያ እናቶችና ያልተከተቡ ህጻናት


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

የሶማሊያ ጤና ባለሥልጣናት ብዙ ሰዎች የኮቪድ-19ን በመፍራት ወደ ክሊኒኮችና ሆስታሎች መሄድ ስለሚፈሩ፣ የእናቶች ጤና ምርመራና የህጻናት ክትባት በከፍተኛ ቁጥር መቀነሱን ተናግረዋል፡፡የጤና እንክካቤ ሠራተኞቹ ለነፍሰ ጡር እናቶችና ህጻናት እንክብካቤ ሲቀንስ የተለመዱት የዘወትር ጤና ችግሮች ይባባሳሉ፡፡ ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በበለጠ ብዙ ሰዎች ሊጎዱ እንደሚችሉም ተናግረዋል፡:

አሚና ሙስታፍ እና ቤተሰቦችዋ ጎርፍ ካፈናቀላቸው ሦስት ዓመት አለፋቸው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መኖሪያቸው የሞቋዲሾው መጠለያ ጣቢያ ሆኗል፡፡ ሶስት ሳምንት የሞላው ልጇ ክትባት ያስፈልገዋል፡፡ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ ግን ወደ ህክምና መስጫ ጣቢያዎቹ መሄድ አልደፈረችም፡፡ ይሄ ፍርሃት እሷ ባለችበት የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ባሉት ሰዎች ሁሉ ያደረ መሆኑን ትናገራለች፡፡ እንዲህ ትላለች አሚና

እኔ ወደ ጤና እንክባቤ መስጫ ተቋማቱ መሄድ አልቻልኩም፡፡ ምክንያቱም ኮቪድ-19 መላውን ዓለም እየወረረ ነው፡፡ ለራሴም ሆነ ለልጄ ጤንነት እፈራለሁ፡፡ ወደ ጤና ተቋማቱ በመሄድ ቫይረሱ እንዲይዘን አንፈልግም፡፡ በዚሁ በኮቪድ-19 የተነሳ እኔም ሆንኩ ልጄ የቅድመ ወሊድም ሆነ ከወሊድ በኋላ ያለው አስፈላጊ የጤና እንክብካቤ አምልጦናል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።​

በኮቪድ ስጋት ክሊኒኮችን የሸሹ የሶማሊያ እናቶችና ያልተከተቡ ህጻናት
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:39 0:00


XS
SM
MD
LG