በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጋሞ ዞን ተፈናቃዮች በረሃብ እየተሰቃዩ መሆናቸውን ተገለፀ


በጋሞ ዞን ሜሎ ወረዳና ባስኬቶ ልዩ ወረዳ የማንነት ግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ከ37 ሺህ በላይ የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ተፈናቃዮች በረሃብ እየተሰቃዩ መሆናቸውን ገለፁ።

ሰብዓዊ ድጋፍ ተቋርጦ እንደነበረ የወረዳው አስተዳዳሪ ገልፀው በአካባቢው አሁንም የፀጥታ ችግር ስላለ ተፈናቃዮቹን ወደየቀያቸው ለመመለስ መቸገራቸውን አመልክተዋል።

ተፈናቃዮቹ በቂ ድጋፍ እንደማይደረግላቸውና እስከ አሁን በምግብ እጥረት ሰባት ህፃናት መሞታቸውን አስተዳዳሪው ገልፀዋል።

በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት የተቆራረጠ መሆኑን ያሳወቀው የደቡብ ክልል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር “ለተፈናቃዮቹ ድጋፍ የማድረግና ወደየቀያቸው መመለስ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ነው” ብሏል።

ለተጨማሪ ዘገባ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የጋሞ ዞን ተፈናቃዮች በረሃብ እየተሰቃዩ መሆናቸውን ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:01 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG