ጆሃንስበርግ —
እ.አ.አ. በ 1966 ዓ.ም የኒውዮርክ ሴናተር የነበሩት ሮበርት ኬኔዲ (Robert F. Kennedy) በያኔዋ ዘረና ደቡብ አፍሪካ ታሪካዊ ጉብኝት አድርገው ያስተላለፉት የተስፋ መልዕክት እነሆ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በኋላም ማስተጋባቱን ቀጥሏል።
ሮበርት ኬኔዲ በወቅቱ ያደረጉት ንግግር በሕይወታቸው ካደረጉአቸው ሁሉ የሚደነቅ ነው ሲሉ ምሁራን መስክረውላቸዋል።
የኬነዲ ቤተሰብ አባላት የዚያን ታሪካዊ ጉብኝት 50 ዓመት ምክንያት በማድረግ ባሁኑ ወቅት ደቡብ አፍሪካን በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ።
አኒታ ፓወል ተከታዩን አጭር ዘገባ ከጆሃንስበርግ አድርሳናለች። ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል።