በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኤርትራ መሪዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መርማሪ ኮሚሽን አሳሰበ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

ኤርትራ ውስጥ የሚደርሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚመረምረው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚደገፈው ኮሚሽን በዚያች ሃገር መሪዎች ተፈጽመዋል የሚባሉ ወንጀሎችን የሚመረምር ፍርድ ቤት ወይም ልዩ ችሎት እንዲመሰረት ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።

ባለፈው ሰኔ ወር የወጣ አንድ የተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት የኤርትራ መንግሥት መሪዎች ከሃያ በላይ ዓመታት በፊት

“በሰብዓዊ ፍጡራን ላይ ወንጀል ፈጽመዋል” ማለቱ ይታወሳል።

ከመርማሪው ኮሚሽን ሦስት አባላት አንዷ የነበሩትና የመጀመሪያዋ የመንግሥታቱ ድርጅት የኤርትራ ጉዳይ ልዩ ራፖርተር ሺላ ኪታሩት ለቪኦኤ እንዳሉት ኮሚሽኑ በሪፖርቱ የሰዎች ደብዛ ማጥፋት ማሰቃየት፣ ያለፍርድ ሄደት ላልተወሰነ ጊዜ በእስር ማቆየት፣ እንዲሁም ርሸናን ጨምሮ የተለያዩ ኢሰብዓዊ ተግባራት ስለመፈጸማቸው ማስረጃዎችን ዘርዝሮ አቀርቡዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምፅ ያዳምጡ፡፡

የኤርትራ መሪዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መርማሪ ኮሚሽን አሳሰበ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:38 0:00

XS
SM
MD
LG