ዋሽንግተን ዲሲ —
በአማራ ክልል በመተማ ሁለት የወልቃይት ተወላጆች፣ በጎንደር ከተማ ደግሞ አንድ የማክሰኝት ከተማ ተወላጅ በድምሩ ሦስት ወጣቶች ታኅሣሥ 9/2009 በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውንና በትናንትናው ዕለት የቀብር ሥነ- ስርዓታቸው መፈጸሙን ቤተሰብና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ገለጹ።
ነዋሪዎቹ “በክልሉ ሰዎች ይገደላሉ፣ ይታሰራሉ አንዳንዶቹ የደረሱበት አይታወቅም። የክልሉ መንግሥት ለዜጎቹ ምንም የሚያደርገው ጥበቃ የለም ” ይላሉ።
የክልሉ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሡ ጥላሁን በበኩላቸው መንግስት ለዜጎቹ ጥበቃ እንደሚያደርግ ገልጸው ተገደሉ ስለተባሉት ወጣቶች ለጊዜው ከአካባቢው ርቀው ስለሚገኙ "መረጃ የለኝም" ብለዋል።
ጽዮን ግርማ ያጠናቀረችውን ዘገባ ለማድመጥ የተያያዘውን የድምጽ ፋይል ያድምጡ።
አስተያየቶችን ይዩ (10)
ተጨማሪ አስተያየቶችን ለመመልከት ይጫኑ