በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በበደሌና በቢሾፍቱ ተማሪዎች እየታሠሩ መኾኑን ተማሪዎች ገለጹ


በየካቲት ወር በሂርና የተደረገ ተቃውሞ
በየካቲት ወር በሂርና የተደረገ ተቃውሞ

ከተጀመረ አምስተኛ ወሩን ሊደፍን ጥቂት ቀናት የቀረው የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞ በአንዳንድ ከተሞች በሚገኙ ትምሕርት ቤቶች ከትናንት በስቲያ፣ ትናንትና ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማና ደባዩ በተባለ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት እንዲሁም በበደሌ ከተማና ለሊሳ ሃሮ ቶሬ በተባለች የገጠር ቀበሌ ተማሪዎች እንደታሠሩና በአስለቃሽ ጭስ ምክንያት፤ ሆስፒታል እንደገቡ ነዋሪዎችና ተማሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

ከተጀመረ አምስተኛ ወሩን ሊደፍን ጥቂት ቀናት የቀረው የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞ በአንዳንድ ከተሞች በሚገኙ ትምሕርት ቤቶች ከትናንት በስቲያ፣ ትናንትና ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማና ደባዩ በተባለ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት እንዲሁም በበደሌ ከተማና በኢሉአባቦር ለሊሳ ሃሮ ቶሬ በተባለች የገጠር ቀበሌ ተማሪዎች እንደታሠሩና በአስለቃሽ ጭስ ምክንያት፤ ሆስፒታል እንደገቡ ነዋሪዎችና ተማሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

ፖሊስ እና የከተማ መስተዳድሩ ኃላፊዎች መረጃው የተሳሳት እንደኾነ በተለይ በቢሾፍቱ ምንም እንቅስቃሴ እንደሌለ ገልጸዋል፡፡ በኢሉአባቦር ዞን ለሊሳ ሃሮ ቶሬ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት የተወረወረ አስለቃሽ ጭስ አለመኖሩን ገልጸው “ተጎድተው ሆስፒታል የገቡት አንድ ስድስት ተማሪዎች የፖሊስ ዱላ ሲያዩ በድንጋጤ ተረጋግጠው ነው” ብለዋል፡፡

ጃለኔ ገመዳ ያጠናቀረችውን ዘገባ ጽዮን ግርማ ታቀርበዋለች፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

በበደሌና በቢሾፍቱ ተማሪዎች እየታሠሩ መኾኑን ተማሪዎች ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:51 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG