በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኦብነግና የኢትዮጵያ መንግሥት እየተደራደሩ ናቸው


በኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባርና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ለሦስት ቀናት ይቆያል የተባለ ውይይት ትናንት ዕሁድ ተጀምሯል። በኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና በኦብነግ መካከል ንግግሩ የተጀመረው ተለይቶ ባልተገለፀ የኬንያ ከተማ ነው።

ዕሁድ፣ የካቲት 4/2010 ዓ.ም. መጀመሩ የተነገረው ድርድር የንግግሮቹ የመጀመሪያ ዙር እንደሆነ ተገልጿል።

የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር ቃል አቀባይ አብዱልቃድር ሃሰን ሂርሞጌ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ሁለቱም ወገኖች አራት አራት ልዑካንን ወደ ኬንያ ልከዋል።

የኦብነግ ልዑካን ቡድን የተመራው በውጭ ጉዳዮች ኃላፊው አብዲራህማን ማኅዲ እንደሆነ ተገልጿል። በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ግን መሪው ማን እንደሆነ አይታወቅ እንጂ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሐመድ ኦማር ከሌሎች ባለሥልጣናት ጋር እንደነበሩ የውይይቱ አመቻቾች ያወጡት ፎቶግራፍ ያሳያል።

ለንግግር የቀረቡት በርካታ ጉዳዮች መሆናቸውን ለቪኦኤ የገለፁት ቃል አቀባዩ ሂርሞጌ በርህ፣ በካሣ፣ እራስን በራስ ማስተዳደር፣ በነፃነት፣ በውሣኔ ሕዝብ፣ በምጣኔ ኃብትና ለመቶዎች ዓመታት በዘለቀ ወረራ ባሉት ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ አመልክተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ኦብነግና የኢትዮጵያ መንግሥት እየተደራደሩ ናቸው
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:07 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG