አዲስ አበባ —
ከያዝነው የፈረንጆች ወር በኋላም ቢሆን አቅርቦት የሚቋረጥባቸው የድርቅ ተረጂዎች እንደማይኖሩ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሺነር አስታወቁ፡፡
ኮሚሺነሩ አቶ ምትኩ ካሣ ለአሜሪካ ድምፅ እንዳስረዱት በሰኔ ወር መጨረሻ አቅርቦቱ ያልቃል በሚል የተገለፀው በዓለም ምግብ ፕሮግራም የሚረዱትን አንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ዜጎች ብቻ የሚመለከት ነው፡፡
ለእነዚህ ዜጎቻችን የሚደረገው ድጋፍም በመንግሥት አልያም በለጋሾች አማካኝነት ይቀጥላል ብለዋል ኮሚሺነሩ፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ