በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያና ኤርትራ - የሁለት ጎረቤታሞች ታሪክ፣ ፖለቲካ ለውጥ ዕድሎችና ፈተናዎች


የኢትዮጵያና ኤርትራ ጉዳይ
የኢትዮጵያና ኤርትራ ጉዳይ

“እንደ እኔ አስተያየት አሁን ዋናው መመለስ ያለበት ጥያቄ በምን መልክ በኤርትራና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውሕደት ሊፈጠር ይችላል የሚለው ነው። ቁልፉ ኢትዮጵያ እጅ ነው ያለው።” ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ። “አሁን ለተጀመረው ቁልፉን የያዘችው ኢትዮጵያ ናት" በሚለው አልስማም። አሁን የሚደረገው የእርቅ ምመንገድ የተጀመረው በሁለት ብሔረ መንግስታት ልንለው እንችላለን ነው። ስለዚህ ሰጥቶ መቀበልን ከግንዛቤ የሚያስገባ ነው የሚሆነው።”ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀኝ። “ይህ ሁኔታ ዳር እንዲደርስ ሁሉም በየበኩሉ ቀና ለሆነው ለውጥ ራሱን ማዘጋጀት አለበት። 'ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ያደርጉልናል' ብለን ቁጭ ብንል ለስኬት የመብቃት ዕድሉ አናሳ ነው የሚሆን።” ፕሮፌሰር ሹመት ሲሻኝ።

ሰሞንኛው ወግ ቀጥሏል።

ያለፈው ሳምንት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኢትዮጵያ ጉብኝትና ደማቅ አቀባበል፤ መሰንበቻውን አሥመራ ላይ የታየው ታላቅ የደስታ ስሜት እና ከዚያ ቀደም ብሎ በተከታታይ እውን የሆኑት ያልተጠበቁ ሁኔታዎች፤ አጠቃላይ ድባቡ በሁለቱ ጎረቤት አገሮች ኢትዮጵያና ኤርትራ ጉዳይ አዲስ ምዕራፍ ከፋች ተደርጎ ተወስዷል።

የተፈጠረውን ሁኔታ ምንነት እና የቀጣዩን ሂደት አቅጣጫዎች ጨምሮ በርከት ባሉ ጭብጥች ዙሪያ የታሪክ ምልከታ ለመፈንጠቅ የታለመ ተከታታይ ውይይት ነው።

ተወያዮች፡- በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጉዳዮች ላይ ሠፊ ጥናት ያካሄዱ የታሪክ ምሁራን ናቸው።

ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀኝ ቀደም ሲል በዩናይትድ ስቴትሱ የኒውዮርክ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ለረዥም ዓመታት በታሪክ መምሕርነት ያገለገሉ የታሪክ ምሁርና የግጭቶች ጥናት ባለ ሞያ ናቸው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በተለያዩ ኃላፊነቶችና በመምሕርነት አገልግለዋል።

ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ የስዊዲኑ የUppsala ዩኒቨርሲቲ ለረዥም ዓመታት በታሪክ መምሕርነትና እንዲሁም በጥናት እና ምርምር አገልግለዋል።

ፕሮፌሰር ሹመት ሲሻኝ በዩናይትድ ስቴትሱ የክርስቶፈር ኒውፖርት ዩኒቨርሲቲ ለረዥም ዓመታት በታሪክ መምሕርነት ያገለገሉና ባሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የትምሕርት ፕሮግራም አማካኝነት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በምርምር እና በማስተማር አገልግሎት ላይ ያሉ ናቸው።

ተከታታይ ውይይቶቹን ከዚህ ያድምጡ።

የሁለት ጎረቤታሞች ታሪክ .. ቆይታ ከሦሥት የታሪክ አጥኝዎች ጋር .. ክፍል አንድ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:20:39 0:00
የሁለት ጎረቤታሞች ታሪክ .. ክፍል ሁለት።
please wait

No media source currently available

0:00 0:21:36 0:00
የሁለት ጎረቤታሞች ታሪክ .. ሦሥተኛና የመጨረሻ ክፍል።
please wait

No media source currently available

0:00 0:18:28 0:00

የቀደሙትን ውይይቶች ለመከታተል ከዚህ በታች የሚያገኙትን አያያዥ ጽሁፍ ይጫኑ፡-https://amharic.voanews.com/a/ethiopia-eritrea-relationship-historical-perspectives-with-professors-shumet-sishagne-and-professor-gebru-tarekegne-voa-alula-kebede-july-20/4482071.html

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG