በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የማሊ የጅሃድ አራማጅ በከፍተኛ ክስ በአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ቀረበ


ፋይል ፎቶ አህመድ አልፋቂ አልማህዲ በአለም አቀፉ ፍርድቤት
ፋይል ፎቶ አህመድ አልፋቂ አልማህዲ በአለም አቀፉ ፍርድቤት

በቲምቡክቱ በሚገኙ ተወዳጅ እድሜ ጠገብ ሃውልቶች ላይ ባደረሰው ውድመት በአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ታሪክ የመጀመሪያ በሆነው የቅርስ ማጥፋት ወንጀል የጅሃድ አራማጁ አህመድ አልፋቂ አልማህዲ ተከሰሰ።

የአልማህዲ ጥፋትና የሚጠብቀው የፍርድ ቅጣት በአስተርጓሚ በተነበበት ጊዜ፤ በእስልምና እምነት ተከታይ ሰዎች ተገፋፍቶ ድርጊቱን እንደፈፀመ ገልጾ ሌሎች ሙስሊሞች የሱን ዱካ እንዳይከተሉም አሳስቧል።

ችሎቱ በአለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት እየቀረበ ያለው የእስልምና አክራሪው አህመድ አልፋቂ አልማህዲ ክስ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። አልማህዲ እ.አ.አ 2012 በሚላ ከተማ ቲምቡክቱ የሚገኙትን ታሪካዊ ሃውልቶችና መስጊዶች በማውደሙ ለተከፈተበት ክስ ጥፋተኛ መሆኑን በማመኑ ፍርድ ቤቱ ውሳኔው በጥቂት ቀናት ውስጥ ያሰማል።

ፋይል-ፎቶ እድሜ ጠገቡ ሙዚየም በእላማዊ ታጣቂዎች ከወደመ በኃላ
ፋይል-ፎቶ እድሜ ጠገቡ ሙዚየም በእላማዊ ታጣቂዎች ከወደመ በኃላ

የአለም አቀፉ የወንጀል ችሎት ዋና አቃቤ ህግ ፋቱ ቤንሶዳ የቲምቡክቱ የባህል ቅርሶችን ላይ የደረሰው ውድመት በሰብዓዊነት ላይ እንደተቃጣ ጥቃት ይቆጠራል በማለት ተናግረዋል።

የአለም አቀፉ የወንጀል ችሎት ዋና አቃቤ ህግ ፋቱ ቤንሶዳ
የአለም አቀፉ የወንጀል ችሎት ዋና አቃቤ ህግ ፋቱ ቤንሶዳ


"ባህል ማንነታችን ነው። ከኛ የቀደሙት ስዕሎችን፣ ቅርፃቅርጾችን፣ ሃውልቶችን፣ ታላላቅ ግንቦችንና ሌሎችም ባህላችንን የሚያንፀባርቁ ስራዎቻቸውን ትተውልን አልፈዋል። ልባቸውንና ነፍሳቸውን በነዚህ የፈጠራ ስራዎቻቸው ላይ አስቀምጠዋል። በጊዜያቸው የነበረውን የባህልና እምነት ለቀጣዩ ትውልድ ያስተላለፉበትም ነው።" ፋቱ ቤንሶዳ

የማሊ የጅሃድ አራማጅ በከፍተኛ ክስ በአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ቀረበ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:58 0:00

XS
SM
MD
LG