በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ ዘንድሮ ዕዳዋን ሳትከፍል ቀረች - ዘገባ፣ ምላሽና ትንታኔ


ኢትዮጵያ ዘንድሮ ዕዳዋን ሳትከፍል ቀረች - ዘገባ፣ ምላሽና ትንታኔ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:05 0:00

ኢትዮጵያ ዘንድሮ ዕዳዋን ሳትከፍል ቀረች - ዘገባ፣ ምላሽና ትንታኔ

ኢትዮጵያ ላለባት ዕዳ ለዓለምአቀፍ አበዳሪዎቿ ዛሬ፤ ታኅሣስ 16 ይጠበቅባት የነበረውን የወለድ ክፍያ ሳትፈፅም መቅረቷ ተገለፀ።

“ሃገሪቱ ወለዱን መክፈል ያልቻለችው አቅም ስለሌላት ሳይሆን ከሌሎች አበዳሪዎች ጋር እየተደረገ ያለውን የብድር እፎይታ ድርድር እንዳይጎዳው በማሰብ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር ደ’ኤታ እዮብ ተካልኝ ለቪኦኤ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስና ኢንቨስትመንት ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ሰውአለ አባተ ደግሞ ሁኔታው መንግሥት በአበዳሪዎች እንዳይታመን ሊያደርገው እንደሚችልና ከፍተኛ የወለድ መጠን እንደሚያስከትል አሳስበዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG