በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያውያን ተራድዖ አሰባሳቢ ባለ አደራ ቦርድ የሚልዮኑን ዶላር እርከን አለፈ


ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያም የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ የአማካሪ ቦርዱን ሊቀ መንበር
ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያም የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ የአማካሪ ቦርዱን ሊቀ መንበር

“የምንሠራውን ነገር በሙሉ በግልጽና በተጠያቂነት ነው የምናደርገው ብለናል። ገንዘብ እንዴት እንደምንሰበስብ፣ ማን እንደሰጠ ማን እንዳልሰጠ ሁሉ ነገር ግልጽ ነው። እኛ ብቻ የምናወራውን ሳይሆን .. የተሰበሰበውን መረጃ ተመልክቶ ከየት እንደመጣ .. ራሱ አይቶ እንዲገነዘብ ነው።” ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያም የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ የአማካሪ ቦርዱን ሊቀ መንበር።

Ethiopian Diaspora Trust Fund በሚለው የእንግሊዝኛ መጠሪያው የሚታወቀው በውጭ አገሮች ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ ልማት መርጃ የሚውል ገንዘብ የሚያሰባስበው ባለ አደራ ቦርድ እስካሁን ያሰባሰበው ገንዘብ ከአንድ ሚልዮን ዶላር መብለጡን ይፋ አደረገ።

“አንድ ዶላር በቀን” ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አሕመድ ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ የተዋቀረው ቡድን ለውጥኑ መሳካት ያለውን ተሥፋና “አሉ” ያላቸውንም ፈተናዎች ጠቁሟል። ይህንኑ ዜና መሠረት በማድረግ በአዲሱ ዓመት ዋዜማ የአማካሪ ቦርዱን ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያምን አነጋግረናል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

የኢትዮጵያውያን ተራድዖ አሰባሳቢ ባለ አደራ ቦርድ የሚልዮኑን ዶላር እርከን አለፈ
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:27 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG