በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ ምክር ቤት አማካሪዎች የወራት ክንውንና የነገ ትልሞች


የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ ምክር ቤት አማካሪዎች
የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ ምክር ቤት አማካሪዎች

"ይህ የTrust Fund ይህ ውጥን ገንዘብ ስለ ማሰባሰብ ብቻ አይደለም። ያሉንን የተለያዩ የሃይማኖት፣ የባሕልና የዘውግ መሠረቶቻችንን በመጠቀም፤ ልዩ-ልዩ ተሞክሮዎቻችንን ለላቀ ጥቅም ማዋል የምንችልበትን መንገድ መፍጠር ጭምር እንጂ" ዶ/ር መና አክሊሉ ደምሴ የመማክርት ጉባኤው ዋና ጸሃፊ።

አሥራ ስምንቱ የመማክርት ጉባኤው አማካሪዎች ከፊሉ የተሳተፉባቸው ሁለት መድረኮች መሰንበቻውን ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ተስተናግደዋል።

በአካባቢው ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ጋር የተወያይው ምክር ቤት በዓለም አቀፍ ደረጃ ገንዘብ ማሰባሰብ የሚያስችል ፈቃድ የሚያገኝበትን ሕጋዊ ሕልውና ጨምሮ ሥራውን በብቃት ለማከናወን የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥራዎችን ሲሠራ መቆየቱን አስታውቋል።

የድርጅቱን የዕለት-ተዕለት ሥራ የሚያስፈጽምና በዲሬክተሮች ቦርድ የሚመራ ጽ/ቤት ስለሚቋቋምበት ሁኔታ፤ የሚሰበሰበው የአደራ ገንዘብ ለምን ዓይነት ሥራዎች እንደሚውል ስለሚታቀድበት ግልጽነትና ተዓማኒነት ያለው አሠራር፤ ስለ ወጣቶች የጎላ ተሳትፎና በቴክኖሎጂ የሚደገፉ አዳዲስ ቀልጣፋ አሠራሮችን ለማስተዋወቅ ያላቸውን ውጥን አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል።

በረሃብና ቸነፈር የሚሰቃዩ ሕጻናትን እምባ ለማበስ በአንድ ብር እርዳታ ተፈትነናል” ሲል የጥያቄውን ምንነት ያስረዳው ደግሞ በጋዜጣዊ መግለጫው ከተሳተፉት የአማካሪ ቡድኑ አባላት አንዱ አርቲስት ታማኝ በየነ ነው።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

የኢትዮጵያውያን ተራድዖ ባለ አደራ ምክር ቤት አማካሪዎች የወራት ክንውንና የነገ ትልሞች
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:30 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG