በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዲሞክራሲ በተግባር


ማሪን ሎ ፔን
ማሪን ሎ ፔን

በአውሮፓ ኅብረት ህልውና ላይ ጎጂ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ አሳድሮ የነበረው የፈረንሳይ ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ውጤት በቀኝ አክራሪው ብሄርተኛ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ ማሪን ሎ ፔን መሸነፍ ተወግዷል።

በአውሮፓ ኅብረት ህልውና ላይ ጎጂ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ አሳድሮ የነበረው የፈረንሳይ ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ውጤት በቀኝ አክራሪው ብሄርተኛ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ ማሪን ሎ ፔን መሸነፍ ተወግዷል።

ሎ ፔን ፈረንሳይን ከአውሮፓ ኅብረት አባልነቷ የማስወጣት ፍላጎት ያላቸው ሲሆኑ በስደተኞች ላይም ጥሩ አመለካከት የላቸውም።

በምርጫው ያሸነፉት ኢማኑኤል ማክሮን ከናፖሊዮን ቦናፓርት ወዲህ ለፈረንሣይ በዕድሜያቸው እጅግ ወጣት የሆኑ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ናቸው። ፈረንሳይን አንድ ለማድረግ በአውሮፓ ኅብረት አባልነታቸው ለመቀጠልና በዩሮ መገበያየታቸውን ለመቀጠል ቃል ገብተዋል።

የቀኝ አክራሪ ብሄርተኛ ፓርቲዎች ፈረንሳይን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሃገሮች በተካሄዱ ምርጫዎች ሽንፈት እየገጠማቸው ነው። ሁኔታው ባጠቃላይ ለዓለም በተለይ ግን ለአፍሪካ ምን አንድምታ ይኖረዋል?

የምሽቱ “ዲሞክራሲ በተግባር” ፕሮግራም ባጭሩ ይመለከተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ዲሞክራሲ በተግባር
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:59 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG