ዋሺንግተን ዲሲ —
በባሕር ዳር ከተማ በዛሬው ዕለት በቤት ውስጥ የመዋል አድማ ተደርጎ ዋለ።
ባለፈው ዓመት በዛሬዋ ቀን በአካባቢው በተካሄደው ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት የተገደሉትን ለማስታወስ የተደረገ መሆኑንም የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይገለፅ የጠየቁን አስተያየት ሰጪ የአሜሪካ ድምፅ ማምሻውን ካነጋገራቸው ውስጥ አንዱ ናቸው።
በተመሳሳይ ምክንያት ድምፃቸው ሆን ተብሎ የተቀየረ መሆኑን ለመጠቆም እንወዳለን።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ