በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጥቃት ደረሰበት


በእንግሊዝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ /ለንደን/
በእንግሊዝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ /ለንደን/

ለንደን የሚገኘው በእንግሊዝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዛሬ፤ ማክሰኞ ሰኔ 23/2020 ዓ.ም. ጥቃት እንደተፈፀመበት የሚሲዮኑ ምክትል መሪ አምባሳደር አባቢ ደምሴ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

“በድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት የተቆጡ ብረትና ተቀጣጣይ ነገሮችን የያዙ” ያሏቸው ሃምሳ የሚሆኑ ወጣቶች ኤምባሲውን መውረራቸውን፣ የሃገሪቱን ባንዲራ አውርደው ሌላ ባንዲራ መስቀላቸውን፣ ሲወጣ ያገኙትን አንድ ተገልጋይ መደብደባቸውን፣ በሩን በኃይል ጥሰው ለመግባትና ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን፣ መስኮት መስበራቸውን ገልፀዋል።

አምባሳደር አባቢ ደምሴ
አምባሳደር አባቢ ደምሴ

አምባሳደሩ ፖሊስ መጥራታቸውንና ለእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ደውለው የጥበቃና የፀጥታ ድጋፍ መጠየቃቸውንና በሥፍራው የተገኙት የፖሊስ አባላት አስፈላጊ ናቸው የሚሏቸውን መረጃዎች መሰብሰባቸውን ተናግረዋል።

መሉውን ቃለ ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጥቃት ደረሰበት
please wait

No media source currently available

0:00 0:15:59 0:00


XS
SM
MD
LG