በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የእግር ኳስ ተጫዋቹ አሰግድ ተስፋዬ አረፈ


የእግር ኳስ ተጫዋቹ አሰግድ ተስፋዬ /ፎቶ ኢንተርኔት/
የእግር ኳስ ተጫዋቹ አሰግድ ተስፋዬ /ፎቶ ኢንተርኔት/

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን፤ እንዲሁም የቡና፣ የመድንና የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦች ተሠላፊ የነበረው አሰግድ ተስፋዬ ዛሬ /ቅዳሜ ግንቦት 26/2009 ዓ.ም./ ረፋድ ላይ በድንገት አርፏል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን፤ እንዲሁም የቡና፣ የመድንና የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦች ተሠላፊ የነበረው አሰግድ ተስፋዬ ዛሬ /ቅዳሜ ግንቦት 26/2009 ዓ.ም./ ረፋድ ላይ በድንገት አርፏል፡፡

አሰግድ ወድቆ ሕይወቱ ያለፈው አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ የቀበሌ ሃያ ሦስት ሜዳ ተብሎ በሚጠራው ሜዳ ላይ ለሰውነት ማነቃቂያ ተጫውቶ ከጨረሰ በኋላ ሰውነቱን ታጥቦ ሲወጣ እንደሆነ በሥፍራው የነበሩ ጓደኞቹ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

የአሰግድ አስከሬን ወዲያው ለምርመራ ወደ ዳግማዊ ምንልክ መታሰቢያ ሆስፒታል መወሰዱና የምርመራ ውጤት እየተጠበቀ መሆኑ ታውቋል፡፡

አሰግድ በቅርቡ ከመሠረተው ትዳር አንድ ልጅ ማፍራቱ ተገልጿል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የእግር ኳስ ተጫዋቹ አሰግድ ተስፋዬ አረፈ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:44 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG