በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕግ ማሻሻያ ያስፈልጋል" - ጦማሪ ዘላለም ክብረት


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ (ፎቶው የተገኘው ከአቶ ፍፁም አረጋ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ኃላፊ ትዊተር ገጽ ላይ የተገኘ ነው)
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ (ፎቶው የተገኘው ከአቶ ፍፁም አረጋ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ኃላፊ ትዊተር ገጽ ላይ የተገኘ ነው)

"ለውጡ እንዳይቀለበስ በጥንቃቄ ሊያዝ ይገባዋል"- አቶ ዮናታን ተስፋዬ "እስረኖች በሙሉ ሊፈቱ ይገባል"- ጦማሪ ጌታቸው ሽፈራው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ከእስር እንዲለቀቁ መወሰናቸውና ከዚያም በቤተመንግሥት ለውይይት መጋበዛቸው በመብት አራማጅ ወጣቶች ዘንድ እንዴት ይታያል? በሚለው ጥያቄ ዙሪያ ሦስት ወጣቶችን ያነጋገረቸው ጽዮን ግርማ ተከታዩን አጠናቅራለች።

ከየመን ሰንዓ ዓየር ማረፊያ ተወስደው ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ እስር ቤት የቆዩትና ከትናንት በስቲያ ከእስር የተለቀቁት የአርበኞች ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋራ ቤተመንግሥት ተገናኝተው መነጋገራቸውና ሁለቱ ተጨባብጠው የሚያሳየ ፎቶ ግራፋቸው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በይፋ ከወጣ በኋላ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ በደቂቃዎች ውስጥ በብዙ ሰዎች ገጽ ላይ የተዘዋወረ ነበር።

በኢትዮጵያ ሕገመንግሥታዊነት እንዲከበር ጥያቄን የሚያነሱና በተለያየ ጊዜ ታስረው የተፈቱ ሦስት ወጣት የመብት አራማጆችን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ስለሚያከናውኑት ተግባራት ያላቸውን አስተያየት ጠይቄያቸዋለሁ። በተለይ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የተሰጠውን ውሳኔና በቤተመንግስቱ ውስጥ ያደረጉት ውይይትና የታየው የአብሮነት ፎቶ ግራፍ ለቀጣዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ የሚኖረውን ትርጉም አስተያየት ሰጥተውበታል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ)

"የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕግ ማሻሻያ ያስፈልጋል" - ጦማሪ ዘላለም ክብረት
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:27 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG