መቀሌ —
የትግራይን ክልል ከአማራ ክልል የሚያገናኘው አላማጣ ቆቦ መስመር ለተሽከርካሪዎች ከተዘጋ 4 ቀናት አስቆጥሯል። መንገዱ የተዘጋው በአላማጣ ከተማ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ከተማ ወጣቶች ነው ተብሏል።
የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምርያ እንዳስታወቀው ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ውይይት እየተካሄደ ነው።
የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው - መንገዱ በመዘጋቱ ለስራቸውን እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ