በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከዩክሬን እህል ጭኖ የተነሳው መርከብ የቱርክን ፍተሻ አልፏል


“ራዞኒ” ተብሎ የሚጠራው፣ የሲየራሊዮንን ባንዲራ የሚያውለበልበው 26 ሺህ 527 ቶን ወይም ከ265 ሺህ በላይ ኲንታል በቆሎ ጭኖ ከዩክሬን ኦዴሳ የተነሳው መርከብ ቱርክ ኢስታንቡል አቅራቢያ ጥቁር ባህር ከኪሊዮስ አካባቢ
ይታያል፤ እአአ ነሃሴ 2/2022
“ራዞኒ” ተብሎ የሚጠራው፣ የሲየራሊዮንን ባንዲራ የሚያውለበልበው 26 ሺህ 527 ቶን ወይም ከ265 ሺህ በላይ ኲንታል በቆሎ ጭኖ ከዩክሬን ኦዴሳ የተነሳው መርከብ ቱርክ ኢስታንቡል አቅራቢያ ጥቁር ባህር ከኪሊዮስ አካባቢ ይታያል፤ እአአ ነሃሴ 2/2022

ሃያ ስድስት ሺህ ቶን ወይም ከ265 ሺህ በላይ ኲንታል በቆሎ ጭኖ ከዩክሬን ኦዴሳ ወደብ ከትናንት በስተያ፤ ሰኞ የተነሳው መርከብ ዛሬ በቱርክ የተደረገበትን ፍተሻ አልፎ ጉዞውን ወደ ሊባኖስ ቀጥሏል። ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ እህል ጭኖ ከዩክሬን በተነሳው በዚህ መርከብ ላይ ዘጠና ደቂቃ የቆየ ፍተሻ ማድረጋቸውን የቱርክ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

መርማሪዎቹ የተውጣጡት ከዩክሬን፣ ከሩሲያ፣ ከቱርክና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሲሆን እነዚሁ ወገኖች በዓለም ላይ የተፈጠረውን የምግብ ቀውስ ለማርገብ የሚያችል እህል ከዩክሬን እንዲወጣ ለማድረግ ባለፈው ወር ስምምነት ላይ ደርሰው ነበር።

የዩክሬን መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንዳለው ሌሎች 17 መርከቦች ተጭነው ዩክሬንን ለመልቀቅ ፈቃድ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ከአውስትራሊያውያን ተማሪዎች ጋር ዛሬ በቪዲዮ የተወያዩት የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ “የመጀመሪያው ጭነት ምንም ማለት አይደለም፤ እህል መጫኑ ይቀጥላል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።

XS
SM
MD
LG