በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የእስራኤል ፖሊሶች በአልጀዚራ ጋዜጠኛዋ ቀብር ላይ አስከሬኗን ተሸክመው ከነበሩት መሃል አንደኛውን ማሰራቸው ተገለጠ


የእስራኤል ፖሊሶች በአልጀዚራ ጋዜጠኛዋ ቀብር ላይ አስከሬኗን ተሸክመው ከሚጓዙ ጋር ግጭት ፈጥሩ እአአ ግንቦት 13/2022
የእስራኤል ፖሊሶች በአልጀዚራ ጋዜጠኛዋ ቀብር ላይ አስከሬኗን ተሸክመው ከሚጓዙ ጋር ግጭት ፈጥሩ እአአ ግንቦት 13/2022

ዌስት ባንክ ጂኒን ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትታ የተገደለችው የአልጀዚራ ጋዜጠኛ ሽሪን አቡ አክሌ ቀብር ላይ አስከሬኗን ተሸክመው ከነበሩት አና በእስራኤል ፖሊሶች ከተደበደቡት ፍልስጣኤማውያን መካከል አንደኛውን የእስራኤል ፖሊሶች ያሰሩት መሆኑን ጠበቃው ገለጹ፡፡

አቡ ኻድር መታሰሩን የፖሊስ ቃል አቀባይ አረጋግጠው ሆኖም የታሰረው ከአርቡ የቀብር ሥነ ስርዓት ጋር በተያያዘ አይደለም ብሏል፡፡ ለምን አንደታሰረ ግን አልገለጠም፡፡

በአርቡ የሺሪን አቡ አክሌ ቀብር ላይ የአስራኤል ፖሊሶች አስከሬኗን የተሸከሙትን ሰዎች በቆመጥ ሲደበድቡ አና ባንድ ወቅት አስከሬኑ ሊወድቅባቸው ደርሶ አንደነበር የሚያሳዩት የቪዲዮ ምስሎች በዓለም ዙሪያ በስፋት መወገዙ ይታወሳል፡፡

የአልጀዚራዋ ጋዜጠኛ በዌስት ባንክ የአስራኤል የጦር ኃይል ወርሮት በነበረ ስፍራ በመዘገብ ላይ አንዳለች በጥይት ተመትታ መገደሏ ቁጣ ቀስቅሷል፡፡

XS
SM
MD
LG