አዲስ አበባ —
ከውጊያ ቀጠናው ከአንድ ሳምንት በፊት “12 የህወሓት የጦር ከፍተኛ መኮንኖች እንዲወገዱ ተደርጓል” ሲል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት ዛሬ አስታውቋል። ተዋጊዎቹ እጃቸውን እንዲሰጡ የመከላከያ ኃይሉ እያሳሰበ መሆኑንም አመልክቷል።
በአማራና በአፋር ክልሎች በጦርነቱ ምክኒያት ከ1.8 ሚሊዮን በላይ ቁጥር ያለው ሰው መፈናቀሉንም የፅህፈት ቤቱ የፕሬስ ኃላፊ ቢል ለኔ ስዩም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ገልፀዋል።
የህወሓት ባለሥልጣናት ግን አካባቢዎቹን እየለቀቁ የወጡት በራሳቸው ዕቅድ መሠረት መሆኑን መናገራቸውን ቀጥለዋል።