የትግራይ ክልልን መነሻ ባደረገው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ተፈናቅለው በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዜጎች፣ “ይኣክል”(ይበቃል) በሚል መሪ ቃል ለሦስት ቀናት የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ እየተካሔደ ነው።
በመጠለያ ካምፕ ለአራት ዓመታት እንደቆዩ የሚናገሩት ተፈናቃዮቹ፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በአስቸኳይ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ ይደረግ ዘንድ ጠይቀዋል። የክልሉ አመራሮች "ክደውናል፤ በተፈናቃዮች ሥቃይ እየተጫወቱ ናቸው፤" በማለትም ከሰዋል።
በጉዳዩ ላይ መግለጫ ያወጣው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በበኩሉ፣ ተፈናቃዮቹ በተቃውሞ ሰልፍ ያሰሙትን አቤቱታ እንደሚደግፈው ገልጾ ወደ ቀዬኣቸው ለመመለስ ከወትሮው በተለየ ጠንክሮ እንደሚሠራ አስታውቋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም