በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ አዲስ ፕሬዝዳንት ሰየመች


ኢትዮጵያ አዲስ ፕሬዝዳንት ሰየመች
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:09 0:00

ኢትዮጵያ አዲስ ፕሬዝዳንት ሰየመች

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ስድስተኛው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሹመዋል

ዛሬ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም. በተካሄደው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ አዲሱን ኃላፊነታቸውን የተቀበሉት አምባሳደር ታዬ ፣ ከተሰናባቿ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋር የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።

አዲሱ ፕሬዝደንት ከስልጣን ርክክቡ በኋላ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር የጀመሩት፣ ኢትዮጵያ ያለችበትን የሰላም ዕጦት ቀውስ በማንፀባረቅ ነው፡፡ መንግሥት ከማንኛውም አካል ጋራ ለሰላም ንግግር ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሆኖም ግን “የኃይል አማራጭን በሚጠቀሙ አካላት ላይ ከዚህ በኋላ የመንግሥት ልበ ሰፊነት እጅግ የጠበበ ነው” ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህን ንግግር ያደረጉት በአማራ ክልል በሚንቀሳቀሰው የፋኖ ታጣቂ ኀይል ላይ መንግሥት የተጠናከረ እርምጃ መጀመሩን ከገለፀ ከቀናት በኋላ ነው፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG