ፌስቡክን የሚያስተዳድረው ሜታ በኢትዮጵያ ለሚፈፀሙ ሰብዓዊ መብት ረገጣዎች አስተዋጽኦ አድርጓል ሲል፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው የሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪ ተቋም በቅርቡ ያወጣው ሪፖርት ከሷል። በተለይም ፌስቡክ መረጃዎች ለማሰራጨት የሚጠቀምበት ቀመር፣ ጓጂ መረጃዎች ጎልተው እንዲወጡ ማድረጉንም አመልክቷል። የማህበራዊ ሚዲያ አጥኚዎች እና ተመራማሪዎችም፣ ሆን ተብለው እና ባለማወቅ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች በንፁሃን ዜጎች ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆናቸውን አመልክተው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚፈፀሙ ግጭቶች መባባስ ምክንያት መሆናቸውን ገልጸዋል። ስመኝሽ የቆየ በዚህ ዙሪያ ሰፋ ያለ ዘገባ አላት።
(ዝርዝሩን ከተያያዘው የቪዲዮ ዘገባ ያገኛሉ)
መድረክ / ፎረም