በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሸገር ከተማ አስተዳደር “100 ሺሕ አቤቱታዎች መቅረባቸውን አላውቅም”


የሸገር ከተማ አስተዳደር “100 ሺሕ አቤቱታዎች መቅረባቸውን አላውቅም”
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:23 0:00

የሸገር ከተማ አስተዳደር “100 ሺሕ አቤቱታዎች መቅረባቸውን አላውቅም”

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ በሸገር ከተማ “ሕገ ወጥ ግንባታ” በሚል እየተካሔደ ካለው የቤቶች ፈረሳ ጋራ የተያያዙ፣ 100ሺሕ አቤቱታዎች እንደቀረቡለት ሲናገር፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ደግሞ ይህን ያህል ቅሬታ እንዳልቀረበለት ገልጿል።

የሸገር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጉግሳ ደጀኔ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ “100ሺሕ አቤቱታዎች” የሚለው መረጃ፣ ውይይት ያልተደረገበት፣ በአግባቡ ያልተጣራና ከአንድ ወገን ብቻ የተገኘ ነው፤ ብለዋል፡፡

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ግን፣ በጉዳዩ ዙርያ ከከተማዋ ባለሥልጣናት ጋራ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በተቋሙ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ሓላፊ ተወካይ አቶ ተሾመ ያሚ፣ ከሕዝብ ቀረቡ ከተባሉት አቤቱታዎች ጋራ በተያያዘ፣ ከሸገር ከተማ ሓላፊዎች ጋራ ውይይት መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡

XS
SM
MD
LG