በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዋግ ኽምራና በአፋር ክልል ስር ባሉ የተወሰኑ ቀበሌዎች እርዳታ ማድረስ እንዳልተቻለ ተገለፀ


በዋግ ኽምራና በአፋር ክልል ስር ባሉ የተወሰኑ ቀበሌዎች እርዳታ ማድረስ እንዳልተቻለ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:30 0:00

በዋግ ኽምራና በአፋር ክልል ስር ባሉ የተወሰኑ ቀበሌዎች እርዳታ ማድረስ እንዳልተቻለ ተገለፀ

በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ የሚገኙ ሁለት ወረዳዎችና በአፋር ክልል አስተዳደር ስር ያሉ ሦስት ቀበሌዎች እስካሁን በህወሓት ኃይሎች ቁጥጥር ስር በመሆናቸው ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስም ሆነ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ አለመቻሉ ተገለጸ፡፡

ከሐምሌ 6/2013 ዓ.ም ጀምሮ መፈናቀላቸውን የገለፁት የአበርገሌና ጻግብዥ ወረዳ ተፈናቃዮች በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ያሉበት ሁኔታ አስከፊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን በሁለቱ ወረዳዎች ሰብአዊ ርዳታውን ለማድረስ ከዓለም አቀፍ ረጅ ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በአፋር ክልል ኪልበቲረሱ ዞን መጋሌ ወረዳም በተመሳሳይ ሁኔታ የህወሓት ኃይሎች ሦስት ቀበሌዎች ውስጥ መኖራቸውን የሚናገሩት አስተያየት ሰጭዎች ይህም ለሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦትም ሆነ ለጸጥታ ችግር እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

XS
SM
MD
LG