በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ድሮኖች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት አደረሱ ተባለ


ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ድሮኖች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት አደረሱ ተባለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:41 0:00

ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ድሮኖች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት አደረሱ ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን መነሲቡ ወረዳ መንዲ ከተማ ውስጥ ረቡዕ ጥቅምት 30/2015 ዓ.ም በሰው አልባ አውሮፕላኖች ወይም ድሮኖች ተፈፀመ በተባለ ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች መጎዳታቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።

ዕለቱ የገበያ ቀን በመሆኑም ጥቃቱ ሲፈፀም በርካታ ሰዎች በቦታው እንደነበሩ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። የኦሮሞ ነፃነት ጦር ዓለም አቀፍ ቃል አቀባይ አቶ ኦዳ ተርቢ ጦራቸው መንዲ ከተማን መቆጣጠሩን ገልፀው የድሮን ጥቃቱ በሰላማዊ ሰዎች ላይ እንጂ በእነርሱ ላይ ጥቃት አላደረሰም ሲሉ አስተባብለዋል።

በጉዳዩ ላይ ከፌደራል መንግሥት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። አንድ የኦሮሚያ ክልል ባለሥልጣን ሸኔ መንዲ ከተማን ተቆጣጥሮ ስለነበረ መንግሥት እርምጃ ሲወስድባቸዉ እንደነበረ ገልፀው በድሮን ጥቃቱ የሸኔ አባላትእንጂ ሰላማዊ ሰዎች እንዳልተጎዱ ተናግረዋል።/ዘገባውን የአፋን ኦሮሞ ዝግጅት ባልደረባ ቱጁቤ ሆራ ነው።/

XS
SM
MD
LG