በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የታላቁ ሩጫ አረንጓዴ ዘመቻ


የታላቁ ሩጫ አረንጓዴ ዘመቻ
please wait

No media source currently available

0:00 0:12:05 0:00

የታላቁ ሩጫ አረንጓዴ ዘመቻ

በአፍሪካ ትልቁ የጎዳና ላይ የአትሌቲክስ ፌስቲቫልም እንደሆነ የሚነገርለት ታላቁ ሩጫ ለ21ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ባካሄደው ውድድር ላይ በጀመረው የአረንጓዴ ዘመቻ ከ 350 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን ደረቅ ቆሻሻ ተሰብስቦ እንደገና ጥቅም ላይ እንዲውል ማድረጉን አስታውቋል። በ21 አመታት ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አረንጓዴ ዘመቻን የተቀላቀለው ታላቁ ሩጫ በቀጣይ በሀገሪቱ ላይ የሚያካሂዳቸው ውድድሮች የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረጉና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሰፉ መሆናቸውንም ገልጿል። ስመኝሽ የቆየ በታላቁ ሩጫ ስለተከናወነው የአረንጓዴ ዘመቻና ጅማሮው ያመጣው ውጤት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ዳግም ተሾመ ጋር ቆይታ አድርጋለች።

XS
SM
MD
LG