በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ ዘመናዊ ቲያትር 100ኛ ዓመት ሊከበር ነው


የኢትዮጵያ ዘመናዊ ቲያትር 100ኛ ዓመት ሊከበር ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:51 0:00

ኢትዮጵያ ውስጥ ዘመናዊ ቲያትር የተጀመረበት 100ኛ ዓመት ሊከበር መሆኑ ተበሰረ፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ስለቲያትር ያገባናል ባሉ አስራአንድ የቲያትር ባለሞያዎች የተመሰረተው ‘ስለቲያትር’ የተሰኘ ቡድን ከኢትዮጵያ የቲያትር ማኅበር ጋር በመተባበር ዓመቱን በሙሉ የሚዘልቅ እና በሃገሪቱ እየተዳከመ የመጣውን የቲያትር ሙያ የሚያነቃቃ መርሃግብሮችን ማቀዱን ይፋ አድርጓል፡፡ በዛሬ ዕለትም ከመገናኛ ብዙሃን ጋር የመጀመሪያውን ውይይት አድርጓል፡፡

XS
SM
MD
LG