በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለጌዴዖ ዘላቂ መፍትኄ ተጠየቀ


ፎቶ ፋይል፡ በጌዲዎ ኮቲት ቀበሌ የሚገኙ ተፈናቃይ
ፎቶ ፋይል፡ በጌዲዎ ኮቲት ቀበሌ የሚገኙ ተፈናቃይ

ፌደራል መንግሥቱ ለጌዴኦ ቀውስ ግልፅና ዘላቂ መፍትኄ እንዲሰጥ የጌዴዖ ምሁራን ማኅበር ጠይቋል። በሕዝቡ ላይ ለደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ተመጣጣኝ ትኩረት በክልልና በፌደራል መንግሥት ባለመሰጠቱ ችግሩ የከፋ መሆኑን በመግለፅ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የመከሩት ምሁራን መንግሥትን በምክንያትነት ከስሰዋል።

ሲቪሎችን የገደሉ፣ ያፈናቀሉና ንብረት ያወደሙ ግለሰቦችን መንግሥት ይዞ ሕግ ፊት እንዲያቀርብም ጠይቀዋል።

በሺሆች የሚቆጠሩ የጌዴዖ ብሔረሰብ አባላት አሁንም ችግር ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ለ364 ሺህ ሰው ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ የጌዴዖ ዞን አስተዳዳሪ አሳስበዋል።

የብሄራዊ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ተፈናቃዮችን ከበልግ እርሻ ወቅት በፊት ወደየቀያቸው ለመመለስ የሚያስችል ጥረት እያደረገ መሆኑንና ዲላ ከተማ ላይም ማዕከል ማቋቋሙን ገልጿል።

(ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።)

ለጌዴዖ ዘላቂ መፍትኄ ተጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:52 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG