በሲየራሊዮን በኢቦላ የተጠቃ ሁለተኛ ሰው መገኘቱን የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ

  • ቆንጂት ታየ

ፋይል ፎቶ - በሞንሮቭያ ላይቤርያ የጤና ጥበቃ ሰራተኛ የሰዎችን ትኩሳት በመለክያ ማእከል እየለካ እአአ 2016 (አሶሽየትድ ፕረስ/AP Photo)

የመጀመሪያው የኢቦላ ተጠቂ ባለፈው ሳምንት ይፋ የተደረገው በቅርቡ ታመው ያረፉ አንዲት ሴት አስከሬን ሲመረመር ቫይረሱ ከተገኘ በኋላ ነው።

ከኢቦላ ነጻ ተብላ ባለፈው ወር በታወጀላት በሲየራሊዮን በበሽታው የተጠቃ ሁለተኛ ሰው መገኘቱን የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ።

በኢቦላ በሽታ የተጠቁ የምእራብ አፍሪካ ሃገሮች የሚያሳይ ሰንጠረዥ

የመጀመሪያው የኢቦላ ተጠቂ ባለፈው ሳምንት ይፋ የተደረገው በቅርቡ ታመው ያረፉ አንዲት ሴት አስከሬን ሲመረመር ቫይረሱ ከተገኘ በኋላ ነው።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢቦላ ቫይረስ በምዕራብ አፍሪቃ ዛሬ በሚያበቃው ዓመት ተሸንፏል

እኚህን ሴት ሲያስታምሟቸው የነበሩ አክስታቸው ላይ ቫይረሱ መገኘቱን የዓለም የጤና ድርጅቱ ቃል አቀባይ አስረድተዋል።

ሴትየዋ የህመሙን ምልክት ማሳየት ከጀመሩ በኋላ ለብቻቸው ተገልለው ክትትል ሲደረግላቸው መቆየቱንና አሁን ህክምና ላይ መሆናቸውን ቃል አቀባይዋ አክለዋል።

የዜና ዘገባችንን ለማዳመጥ ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል ይጫኑ።

Your browser doesn’t support HTML5

በሲየራሊዮን በኢቦላ የተጠቃ ሁለተኛ ሰው መገኘቱን የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ