በጽሑፎቹ በሚያነሳቸው ሐሳቦች የተነሳ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብሎ የሦስት ዓመት እስራት የተበየነበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅምት 3 ቀን የአመክሮ ጊዜው ማለፉንና ከእስር አለመፈታቱን ቤተሰቡና ጠበቃው አስታወቁ።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ተመስገን የአመክሮ ግምጋማ ላይ ተቀምጦ፤ ከስህተቴ ተምሬያለሁ ተጸጽቻለሁ ለማለት አለመፍቀዱና በእስር ላይ ሳለ መብቱን በተደጋጋሚ መጠየቁ በማረሚያ ቤቶች ባለስልጣናት እንዳልተወደደለት የህግ ጠበቃው አቶ አምሃ መኮንን ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ገልጸዋል።
ሔኖክ ሰማእግዜር የተመስገንን ወንድምና ጠበቃውን አቶ አምሃን አነጋግሯል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አመክሮ እንዳልተሰጠው ቤተሰቦቹ ገለጹ